Tuesday, April 12, 2011

ተመስገን ! ጌታ ሆይ

 

ተመስገን ! ጌታ ሆይ

አንተ ያረክልን
መች ከሆድ ይጠፋል
ሞትን ለኛ ሞተህ

እኛን አትርፈሃል ::
ሞትን ለኛ ሞቶ
ለሚያኖረን ጌታ
ምስጋና ይገባዋል
ሁሌ ጠዋት ማታ።
አ እዋፋት ዘምረው
እንሰሳትም ጮ

ሰማይና ምድርም

እንዲሁ ተማክረው
ያመሰግኑሃል
ልባቸውን ከፍተው
::
ይብላኝ ለከሃዲው
ለዚያ ለይሁዳ አምላኬ በስምህ
በክህደት ተጎዳ ::
አረ አንተስ ልዩ ነህ

ፍቅርህ መቼ ያልቃል
ጥሎህም የሄደው
በፍቅርህ ይወድቃል ።
ተመስገን ጌታዬ
ሁሌ ጠዋት ማታ
አንተ ያለም ንጉስ
የሁሉ አለኝታ ።
                                                                       ዳግም
- ፍቅሩ
                                                                         4/12/2011




No comments:

Post a Comment